ጣናነሽ-2 ጀልባ ኢትዮጵያ ገባች


ከይር ዜና:- ከዚህ ቀደም ከጂቡቲ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የጀመረችው የጣናነሽ-2 ጀልባ ለአንድ ወር ተኩል ያህል ተጉዛ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጣለች። 

በጉዞ ወቅት ያጋጠመውን አስቸጋሪ የመንገድ ሁኔታ ለመፍታት የተለያዩ የኢትዮጵያ እና ጅቡቲ የመንግስት አካላት  ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል፡፡

በዚህም የጣናነሽ-2 ጀልባ ከሰዓታት በፊት የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጣ ደወሌ መግባቷን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡