የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 41 ሺህ የመንግስት ሰራተኞችን የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚያደርግ የ25/75 ቤቶች ልማት ፕሮጀክት በጋራ ለማልማት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ይህ ስምምነት በተለይም ለመምህራን ቅድሚያ እንደሚሰጥ ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ እንደገለጹት፤ ስምምነቱ ቤት የሌላቸውን የመንግስት ሰራተኞችን ችግር ለመቅረፍ ያለመ ነው ተብሏል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደተናገሩት ባንኩ ለዚህ ፕሮጀክት 120 ቢሊዮን ብር ብድር ለማቅረብ አቅዷል። የብድሩ ወለድ 14 በመቶ ሲሆን፤ ለ20 ዓመት የሚከፈል መሆኑን አስረድተዋል።